ወደ የሚፈልጉት ቋንቋ ይቀይሩ Translate to different Languages

Wednesday, January 8, 2014

በቴዲ አፍሮ ላይ የተከፈተው ዘመቻ በኢትዮጵያዊነት ላይ የተቃጣው ሰይፍ አካል ነው ዛሬም ሌላ በፀረ-ኢትዮጵያዊነት መልክ አዲስ ዘመቻ ከፍተዋል።''CUT CHRISTIANS NECK BY MENCHA'' NEW TERRORIST MOVEMENT TARGETED ETHIOPIAN CHRISTIANS.


''CUT CHRISTIANS NECK BY MENCHA'' NEW TERRORIST MOVEMENT TARGETED ETHIOPIAN CHRISTIANS has already started its act on opening social media campaign against popular Ethiopian musician Tewodros Ksahun. What will you call such non-human act other than Terrorism.Terrorists must get their lesson very soon!!

''በሜንጫ የክርስቲያኖችን አንገት እንቁረጥ'' በሚል እራሳቸውን የሚጠሩ ቡድኖች  ቴዲ አፍሮ አፄ ምንሊክን በተመለከተ ያልሰጠውን መግለጫ አዛብተው አቅርበው የማኅበራዊ ድህረ ገፆች ዘመቻ ከፍተውበት  እንደነበር ይታወቃል።በ እዚሁ እኩይ ተግባር ላይም ኦህዴድ እና የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ተባብረውበት ''የፍቅር ዘመቻ'' የተሰኘው ኮንሰርቱ እንዲሰረዝ መደረጉ አሁንም በ ልዩ ልዩ ድህረ-ገፆች ሲገለፅ መሰንበቱ ይታወቃል።

''በሜንጫ የክርስቲያኖችን አንገት እንቁረጥ'' የተሰኘው ይህ ቡድን ዛሬም ቴዲ ኢትዮጵያን በአለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠራበትን በኮካኮላ ካምፓኒ የተዘጋጀውን መርሃ ግብር ላይ እንዳይሳተፍ ለማድረግ አዲስ ዘመቻ ከፍተዋል። ይህንን ዘመቻ አለመጀመራቸውን ማስተባበያ በአንዳንድ ድህረ-ገፆች ላይ ቢገልፁም አሁንም የሚደርሱት ዘገባዎች ግን የኢትዮጵያ ስም በብራዚል አደባባይ መጠራቱ በእጅጉ እንዳመማቸው የሚያመላክት ነው።

ይህ ተግባር የቴዲ ጉዳይ ብቻ አይደለም ዘመቻው በኢትዮጵያዊነት ላይ የተቃጣ ሰይፍ አካል ነው።ቴዲ የፈለገውን ሃሳብ የመግለፅ ሙሉ መብት አለው።ቴዲ ባልተናገረው ጉዳይ ቢዘመትበትም መታየት ያለበት ግን ማንም ሰው ማንኛውንም ድርጊት ቅዱስ ወይንም እርኩስ የማለት መብቱ ሊከበር የመገባቱ ሃሳብን የመግለፅ ሙሉ መብት ጉዳይ ነው።ማንም አንገትህን በሜንጫ ልቁረጥ ባይ ተነስቶ የአንድን ግለሰብ መብት እንዲጋፋ ዕድል ልንሰጠው አይገባም።

በሃያ አንደኛው ክ/ዘመን ላይ ሆነው ''የክርስቲያኖችን አንገት በሜንጫ እንቆርጣለን'' ብለው የተናገሩ እና በጉዳዩ ላይ መስማማታቸውን የገለፁ ሁሉ በይፋ ይቅርታ ካልጠየቁ በሚኖሩበት ሀገር ለፍርድ የማይቀርቡበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይችልም።ለእዚህም የሲቪል ማኅበራት ለሚመለከታቸው አካላት የጉዳዩን አደገኛነት የመግለፅ ግዴታ አለባቸው።

ለእያንዳንዱ የሀገራችን ችግር በተናጥል በመፍታት ለውጥ ማምጣት ባይቻልም ችግር መፍትሄን ይወልዳል እና ኢትዮጵያውያን ከመቸውም ጊዜ በላይ በ እዚህ በሉላዊነት (globalaization) ዘመን ለሚነሱ የጋራ ሃገራዊ ጉዳዮች አንድ ድምፅ የሚያሰሙበትን የበየነ-መረብ (internet) ዘመቻዎች እና የመረጃ መለዋወጫ መስመሮቻቸውን ማጠናከር እንደሚጠበቅባቸው አመላካች ነው። በመሆኑም በኅብረተሰባችን ውስጥ ታዋቂነት ያተረፉ አክትቪስቶች ሳይውሉ ሳያድሩ አፋጣኝ ንቅናቄ ማድረግ ''በሜንጫ አንገት እንቁረጥ'' ቡድን አባላት  አሁን ላነሱት ፀረ-ኢትዮጵያ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን ወደፊት ለሚነሱ ሌሎች እኩይ ተግባራት ሁሉ ወሳኝ የሆኑ ምላሾች መስጠት ላይ ማተኮር ይገባቸዋል።

ጉዳያችን ታህሳስ 30/2006 ዓም

No comments:

ሐያ ገዳማት የሚገኙበት በግሪክ የሚገኘው የአቶስ ተራራ ገዳማውያን አኗኗር (ቪድዮ)

ገዳሙ ከሰርብያ፣ሮማንያ፣ቡልጋርያና ሩስያ የመጡ ዓለምን የናቁ መነኮሳት ገድመውበታል።